Liverpool M.K Abune Teklehaymanot Church
Ethiopian Orthodox Tewahdo Church In Liverpool

ሊቨርፑል መካነ ቅዱሳን አቡነ ተክለሃይማኖት ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዩኬና አየርላንድ ሀገረ ስብከት የሊቨርፑል መካነ ቅዱሳን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በማኅበርነት ሰባት ዓመታትን ቆይቷል። በእነዚህ ሰባት ዓመታት ውስጥ ምእመናን የራሳቸው አገልግጋይ እና አጽናኝ ካህን ወይም መምህር ሳይኖሯቸው ከሌሎች ከተሞች በሚመጡ ካህናትና መምህራን በመጽናናት እግዚአብሔርን ዘወትር በማገልገል ቆይተዋል። ከሰባት ዓመታት በኋላ የምእመናኑ ጸሎት ተሰምቶ ልመናቸው ቅድመ እግዚአብሔር ደርሶ  አገልጋይ ካህን ካሉበት እግዚአብሔር ወደዚህ ሥፍራ አመጣቸው። ይህንን ፈቃደ እግዚአብሔር የተመለከቱት በወቅቱ  የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ እንጦንስ አዲስ ከመጡት ካህን ቀሲስ ብርሃኑ ጋር በመነጋገር ቦታውን በቋሚነት እያገለገሉ ምእመናኑን እየባረኩ እና እያጽናኑ በእረኝነት እንዲጠብቁ አደረጉ። በዚህም መሠረት ቅዳሴ ቤቱ ጥር 24 ቀን 2006 ዓ.ም (Feb. 1 2014 GC) በብፁዕ አቡነ እንጦስ ተባረኮ የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ታቦት እንዲገባ የቦታውም ስም መካነ ቅዱሳን አቡነ ተክለሃይማኖት እንዲባል ብሎም የካህኑ የማዕረግ ስም ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ብርሃኑ እንዲባል ተደረገ። ከዚች ዕለት ጀምሮ የሊቨርፑል መካነ ቅዱሳን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ሰፊ የሆነውን መንፈሳዊ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።

እርስዎም ይምጡ ይሳተፉ

 የተለያዩ መርሐ ግብራት ሲኖሩ መጥተው ይሳተፉ ዘንድ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች!

መርሐ ግብራችን

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በየሁለት ሳምንቱ ቋሚ የቅዳሴ መርሐ ግብር ታካሂዳለች

አኃዛዊ መረጃዎች

የምእመናን (የአባላት) ቁጥር
0
የአገልጋይ ካህናት ቁጥር
0
የሰንበት ተማሪዎች ቁጥር
0
በዓመቱ የተጠመቁ ምእመናን
0

የቤተ ክርስቲያናችን አባል ይሁኑ

በሊቨርፑል እና አካባቢዋ የሚኖሩ ከሆነ የቤተ ክርስቲያናችን ቋሚ አባል በመሆን በየጊዜው በሚካሄዱ መርሐ ግብሮች ላይ እንዲሳተፉ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች::

ለቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎት ፈላጊዎች

ቀጣይ መርሐ ግብራት

የቤተ ክርስቲያናችንን ቀጣይ ሙሉ የቅዳሴ አገልግሎት ቀኑን እና ሰዓቱን ለማወቅ

ወቅታዊ መረጃዎች

የዐቢይ ጾም ስድስተኛ ሳምንት – ገብር ኄር / Faithful Servant

በጎ አገልጋይ ለጌታው ታምኝ እንደመሆኑ ‹‹ገብር ኄር›› ይባላል፡፡ ይህም ስያሜ ለዐቢይ ጾም ስድስተኛ ሳምንት እንደተሰጠ የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ይገልጻል፡፡ የስያሜው መነሻ የሚገኘው ደግሞ በዕለቱ ሥርዓተ ቅዳሴ ከሚነበበው በማቴዎስ ወንጌል ክፍል ነው፡፡ (ማቴ.፳፭፥፲፬-፴)ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምሳሌ ካስተማራቸው

የዐቢይ ጾም አምስተኛ ሳምንት – ደብረ ዘይት / Mount Olives

ደበረ ዘይት ትርጉሙ የወራ መብቀያ፣ በወይራ ደን የተሸፈነ ተራራ ማለት ነው። ወይም «ደብር» ማለት «ተራራ» ማለት ሲሆን «ዘይት» ማለት ደግሞ «ወይራ» ማለት ነው። በተገናኝ «ደብረ ዘይት» ማለት የወይራ ዛፍ የሞላበት፣ የበዛበት፣ የይወራ ተራራ ማለት ይሆናል።ከኢየሩሳሌም በስተምሥራቅ የሚገኝ ቦታ የሚገኝ ተራራ ሲሆን በመካከል የቄድሮን ሸለቆ ብቻ ነው

አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ የኢሜል አድራሻዎን ያስገቡ

የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን !